Search
Close this search box.

“በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት እየተካሄደ ነው” በሚል የተሰራጨው መስል የቆየ ነው

የተጠቀሰው መረጃ፦ አንድ የX አካውንት “በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት እየተካሄደ ነው” የሚል ትርጉም ካለው የእንግሊዘኛ ፅሁፍ ጋር በማያያዝ አንድ “ዘግናኝ” ይዘት ያለው ምስል ለጥፏል።

በያኑ፦ ምስሉ (አሁን) በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለን “የዘር ማጥፋት” የሚያሳይ ሳይሆን ከአምስት አመት በፊት በሐሰተኛ መረጃ ምክንያት የደቦ ፍርድ ጥቃት ሰለባ የሆነን ግለሰብ ዘገናኝ ምስል የሚያሳይ በመሆኑ የተጠቀሰው መረጃ ሀሰት ነው።

Zoom Afrika, የሚል ስም ያለው እና ከ274,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የX አካውንት “በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት እየተካሄደ ነው” የሚል ትርጉም ካለው የእንግሊዘኛ ፅሁፍ ጋር በማያያዝ ፎቶ አጋርቷል። ይህም ትዊት ይህ ፅሑፍ እስከሚታተም ድረስ ከ102,000 በላይ እይታዎች እና ከ800 በላይ ገብረ መልስ ሲያገኝ ከ480 ጊዜ በላይ ተጋርቷል። 

ይሁን እንጂ አካውንቱ ፅሁፉን እንዲድግፍለት ያያዘው ፎቶ የቆየ እና በሌላ አውድ ውስጥ የተፈጠረን ክስተት የሚያሳይ ነው።

MFC የጎግል ምስል ማፋለጊያ መሳሪያን በመጠቀም ምስሉን ለማጣራት ባደረገው ጥረት የመጀመሪያው የምስሉ ምንጭ ወይም ባለቤት ማን እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም። ይሁን እንጂ መሳሪያው ይህ ምስል ከአምስት አመታት በፊት የተሰራጩትን ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት መሰራጨቱን ያሳያል።

በመሆኑም ይህ ዘግናኝና አሳዛኝ ክስተትን የሚያሳየው ምስል ከአምስት አመታት በፊት በነሃሴ 6/2010 አ.ም በሻሸመኔ ከተማ በወቀቱ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ዳይሬክተር የነበረውን አቶ ጃዋር መሕመድን እና ለሌሎች የቡድኑ አባላት አቀባበል ለማድረግ በተዘጋጀ ስነ ስርዓት ላይ ከተከሰተ “የደቦ ፍርድ” የተወሰደ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። 

በእለቱም “ቦንብ ይዟል” በሚል ሐሰተኛ መረጃ ምክንያት በአንድ ግለሰብ ላይ በደቦ አሰቃቂ ግድያ በአደባባይ የተፈፀመ ሲሆን ምስሉ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ በስፋት ተዘዋውሯል። (ለአብነትም ይህንንይህንን እና ይህንን ማስፈንጠሪያ ይመልከቱ።)

በመሆኑም ምስሉ በX አካውንቱ እንደተጠቀሰው (አሁን) በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለን የዘር ማጥፋት የሚያሳይ ሳይሆን ከአምስት አመት ከ8 ወራት በፊት በሻሸመኔ ከተማ በሐሰተኛ መረጃ ምክንያት የደቦ ፍርድ ጥቃት ሰለባ የሆነን ግለሰብ ዘገናኝ ምስል የሚያሳይ በመሆኑ የተጠቀሰው መረጃ ሀሰት ነው።

We at the MFC strive to verify misleading and false claims so that people get fact-based information and make an informed decision as well. In the process of our work, accuracy and transparency hold a central role. Therefore, if you see errors in our content, please write to us at [email protected] so that our team will make corrections.

Share post on Social media

See related posts

ABOUT MFC

MultiFactCheck

(MFC) is an independent fact-checking organization which is launched to pin-point, track-down, scrutinize, investigate, interrogate, publish and distribute the factual accuracy of claims made by public figures. MFC’s project has geographical priorities. Our work mainly focuses on nations in the Horn of Africa and their diaspora community who reside abroad. We operates from various regions of Africa, Europe and North America. Through a multitude of professional proficiency, MFC deploys best practices of journalism, scholarship and expertise in order to flag, investigate and publish a fact.

Follow Us